የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቪዛ ካርድ መያዣ /Visa Card Holder/ ሊያቀርቡ የሚችሉ ድርጅቶችን በጨረታ አውዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁ 80/2013/14
1. የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች ማለትም፤
የዕቃው ዓይነት |
መለኪያ |
ተፈላጊው መጠን |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በ ሲፒኦ ወይንም ቅድመ ሁኔታ ባላስቀመጠ የባንክ ዋስትና (ብር) |
የቪዛ ካርድ መያዣ/Visa Card Holder/
|
በቁጥር |
1,000,000 |
30,000.00 |
ሊያቀርቡ የሚችሉ ድርጅቶችን በጨረታ አውዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
2. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ የግብር መለያ ሠርተፊኬት ያላቸው እንዲሁም በመንግሥት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት ውስጥ የተመዘገቡ ሆነው የነዚህን ቅጅ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100.00 / አንድ መቶ /በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ጨረታው ከውጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት (ከ2:00-6:00 እና ከ7:00-10:30) ከሳር ቤት በታች ከቫቲካን ኤምባሲ ትይዩ ዝቅ ብሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲሊቲዎች አስተዳደር ሕንፃ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 101 ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
3. የጨረታ ማስከበሪያ በሲ.ፒ.ኦ ወይም ቅድመ ሁኔታን ባላስቀመጠ ባንክ ጋራንቲ ብቻ ከዚህ በታች ባለው ምድብ መሰረት ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
የዕቃው አይነት |
የገንዘቡ መጠን |
የቪዛ ካርድ መያዣ /Visa Card Holder/
|
ብር 30,000.00 |
4. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ሰነዶች በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰአት በፊት ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው በዚያው ዕለት ሐምሌ 24 ቀን 2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተጠቀሰው ቦታ ለመገኘት ፈቃደኛ ሆነው በተገኙት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል፡፡
6. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
7. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 372 28 47 ወይም በ372 28 58 ወይም በፋክስ ቁጥር 372 28 89 ወይም በባንኩ ድህረ ገጽ www.combanketh.com ወይም 2merkato.com ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡